Monday, March 21, 2016

በወሎና ደቡብ ጎንደር አዲስ ወረርሽኝ ተከሰተ

መጋቢት ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት ምንነቱ እስካሁን ያልታወቀው ወረርሽኝ በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችን አጥቅቷል።በበሽታው የተያዘ ሰው ከፍተኛ ሙቀት፣ ራስ ምታት፣ ሳልና ተቅማጥ እንደሚኖረው የገለጹት ነዋሪዎች፣በሽተኞች እስካሁን ህክምና ባለማግኘታቸው ህይወታቸው በአሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ ገብቷል።

በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ የምግብና የውሃ እጥረት መኖሩ፣ ችግሩን እንዳባባሰው ነዋሪዎች ግልጸዋል።

No comments:

Post a Comment