Wednesday, March 30, 2016

በልምምድ ላይ እያሉ ዘጠኝ ኢትዮጵያዊያን የማራቶን ሯጮች የመኪና አደጋ ደረሰባቸው

መጋቢት ፳፩( ሃያ አንድ ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሰሜናዊ አዲስ አበባ ሱሉልታ መውጪያ አቅራቢያ የማራቶን ልምምድ ሲያደርጉ የነበሩ ኢትዮጵያዊያን ሯጮች ድንገተኛ የሆነ ከባድ የመኪና አደጋ ደረሰባቸው። በአደጋው የ25 ዓመቱ ወጣት አትሌት አሻግሬ ግርማ ወደ ሕክምና ተቋማት ቢወሰድም ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም።

ባለፈው ዓመት በህንድ ማራቶን አራተኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው አትሌት ዳምጠው ታሪኩ በበኩሉ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት በግሩ ላይ ደርሶበት የቀዶ ጥገና ሕክምና ተደርጎለታል። ሌሎችም ሯጮችም ከፍተኛና መጠነኛ አካላዊ ጉዳት አጋጥሟቸዋል።
በተመሳሳይ በሱሉልታ መስመር ላይ በልምምድ ላይ ያሉ አትሌቶች ላይ አደጋ ሲደርስባቸው ይህ የመጀመሪያ ጊዜያቸው አይደለም። ባለፈው ዓመትም አትሌት አለማየሁ ሹምዬ ጨምሮ ሁለት አትሌቶች በመኪና አደጋ መሞታቸው ይታወሳል።
በተጨማሪም በምስራቅ ሃረርጌ ዘጠኝ መንገደኞች ሲሞቱ ከሃያ በላይ የሚሆኑት ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። በጎንደር ከተማ አቅራቢያም በድረሰ ተመሳሳይ አደጋ የአስር ሰዎች ሕይወታቸውን አጥህተዋል። በኢትዩጵያ የመኪና አደጋ የአያሌዎችን ሕይወትና አካል ከሚያሳጡት ውስጥ ከቀዳሚዎቹ ተርታ ይመደባል።

No comments:

Post a Comment