Thursday, March 24, 2016

ኢትዮጵያ በአለማችን በከፋ የሳንባ ነቀርሳ በሽታ ከተጠቁ 20 አገሮች አንዷ መሆኗ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 15 ፥ 2015)

ኢትዮጵያን ጨምሮ 20 የአለማችን ሃገራት በከፋ የሳንባ ነቀርሳ (ቲቢ) በሽታ መፈረጃቸውን የአለም ጤና ድርጅት ሃሙስ አስታወቀ።
በየአመቱ መጋቢት 15 የሚከበረውን የቲቢ (TB) ቀን አስመልክቶ ሪፖርትን ያወጣው የጤና ድርጅቱ እነዚሁ 20 አገራት በበሽታው መዛመት የተነሳ የጤና መሰረተ ልማታቸው ፈተና አጋጥሞት እንደሚገኝ ገልጿል።
ባለፉት አስር አመታት በሃገሪቱ የበሽታውን መስፋፋት ለመቆጣጠር የተለያዩ ጥረቶች ቢያደርጉም አጥጋቢ ውጤት ሊገኝ አለመቻሉን የአለም ጤና ድርጅት በሪፖርቱ አስፍሯል።
በየዕለቱ የአራት ሺ ሰዎች ህይወትን እየቀጠፈ የሚገኘውን የቲቢ በሽታ በቀጣዮቹ 14 አመት ውስጥ ከአለም ለማጥፋት አለም አቀፍ ዘመቻ መክፈቱን ድርጅቱ አክሎ አመልክቷል።

No comments:

Post a Comment