Monday, March 28, 2016

አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ተጨማሪ ክስ ተመሰረተባቸው

መጋቢት ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ገዥው መንግስት የገባላቸውን ዋስትና አምነው ወደ አገር ቤት የተመለሱት የአክሰስ ሪል ስቴት መስራችና ባለቤት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ተጨማሪ አዲስ ክስ የቀረበባቸው ሲሆን፣ በዋስ እንዲፈቱ የተወሰነላቸው ውሳኔም እንዲታገድ በመደረጉ ከእስር ሳይለቀቁ ቀርተዋል። በአቶ ኤርምያስ ላይ የቀረበው አዲስ ክስ በደረቅ ቼክ አጭበርብረዋል የሚል ነው።

የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀደም ብሎ በቀረበባቸው ክስ 500 ሺሕ ብር የዋስትና ገንዘብ አስይዘው ከእስር እንዲለቀቁ የሰጠው ውሳኔ ፖሊስ ባቀረበው ይግባኝ እንዲታገድ ተደርጓል።
አቶ ኤርሚያስ ስለተጠየቀባቸው ዋስትና መጠን ሲጠየቁ፣ ገንዘብ፣ ንብረትም ሆነ ሀብት እንደሌላቸው፣ ቤተሰቦቻቸው እየረዱዋቸው እንደሚኖሩ በመግለጽ፣ ፖሊስ በባንክ ብዙ ገንዘብ እንዳለኝ ጠቅሷልና እሱ ዋስትና ይሁንልኝ ብለው ተናግረዋል።
ከውጭ ወደ አገር ቤት በመግባት በርካታ የንግድ ስራዎችን ያስተዋወቁት አቶ ኤርምያስ፣ በተለያዩ ሰበብ አስባቦች ተጠልፈው እንዲወድቁ መደረጉን ታዛቢዎች ይናገራሉ።

No comments:

Post a Comment