Friday, March 25, 2016

በአዲስ አበባ ውሃ በፈረቃ ማደል ሊጀመር ነው

መጋቢት ፲፮ (አሥራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት በፈረቃ ሊታደል መሆኑን የውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን አስታውቋል። ድርጅቱ በአየር መዛባት ምክንያት በለገዳዲና በድሬ ግድቦች ውስጥ ሲገባ የነበረው ውሃ መጠን በማነሱ በፈረቃ ለማደል መወሰኑን ገልጿል።

የፈረቃ እደላው የካቲት 24 ቀን 2008 ዓ.ም. ይጀምራል። ኢሳት በከተማው ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የውሃ እጥረት ማጋጠሙንና በከተማዋ ነዋሪዎች እለታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ ችግር መፍጠሩን ሲዘግብ ቆይቷል።
ድርጅቱ ችግሩ ከመፈጠሩ በፊት ለምን ሌሎች የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ እንደተሳነው የገለጸው ነገር የለም።

No comments:

Post a Comment