Tuesday, March 15, 2016

በሶስት ክልሎች የኮሌራ ወረሽኝ ተከሰተ

መጋቢት ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በደቡብ ክልል አርባምንጭ ዙሪያ አማሮና አባያ ወረዳዎች በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን ገላን ወረዳና በሶማሌ ክልል ሞያሌ ወረዳዎች ላይ የኮሌራ ወረሽኝ ተከስቷል።

በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር እያሻቀበ በመምጣት ላይ ሲሆን፣ ካለፈው እሁድ ጀምሮ ከ140 በላይ ህሙማን በዚሁ በሽታ ተይዘው ወደ ሆስፒታል መግባታቸውንና ለህሙማኑ የህክምና ማዕከል ተቋቁሞ ዕርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን የአርባ ምንጭ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቀፀላ ለማ መግለጻቸውን አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘግቧል።
የጤና ጥበቃ ሚንስቴር በሽታውን እየተከላከልኩኝ ነው ቢልም የአካባቢው ነዋሪዎች ግን የበሽታው ተጠቂዎቹ ወደ ጤና ተቋም ሳይደርሱ በአጣዳፊ ሁኔታ ሕይወታቸውን እያጡ መሆናቸውን ይናገራሉ።
በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳዎች የንጹህ ውሃ እጥረት በመከሰቱ ሕዝቡ ለውሃ ወለድ በሽታዎች የተጋለጠ ሲሆን፣ የክልሉ መንግስት የነዋሪዎቹን የውሃ ችግር ለመፍታት እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት እርምጃዎችን አልተወሰዱም።

No comments:

Post a Comment