Sunday, August 16, 2015

ሰላሳ ሶስት መኮንኖች ከየታሰሩበት እዝ ተግዘው አለም በቃኝ ተወረወሩ:: (ስም ዝርዝር ተያይዟል::)

የወያኔ ጉጅሌ አገዛዝ 7 መቶአለቆች 5 ሻምበሎች 8 ሻለቆች 13 ኮሎኔሎች በድምሩ 33 የወያኔ መከላከያ ሰራዊት አባላት ከሰሜን እዝ እና ከደቡብ ምስራቅ እዝ ታስረው የነበሩበት መኮንኖች ተግዘው አዲስ አበባ ቃሊቲ አለም በቃኝ ካለፍርድ መወርወራቸው በወታደራዊ ደህንነት መምሪያ ከፍተኛ መኮንን የሆኑ እና እስረኞቹ ተግዘው ወደ አለም በቃኝ ሲወርዱ የተመለከቱ የአይን እማኝ ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል:: የአይን እማኙ እንዳሉት በምድር ጦር የደህንነት ክፍል እና በወህኒ ቤቱ መካከል ከማንም እስረኛ ጋር እንዳይገኛኙ ተደርጎ እንዲታሰሩ በጥብቅ ምስጢር የተረካከቡት እስረኛ ወታደሮች በየእዙ ውስጥ በመንግስት ላይ ታሴራላቹ ወታደሩን ታነሳሳላቹ በሰራዊቱ ውስጥ አለመተማመን እንዲነግስ አድርጋችኋል ሕገ መንግስታዊ መብቶች የሚሉ ጥያቄዎችን ደጋግማቹ ታነሳላቹ ከጠላቶቻችን ጋር አብራቹሃል በሚል ተሰብስበው የታሰሩ እና በእዞቹ አከባቢ ያለውን የአከባቢ ሰላም መደፍረስ እና የወታደሮች ጉርምርምታ በመፍራት ይዘዋቸው ወደ አዲስ አበባ ካለፍርድ አለም በቃኝ እንዳስገቧቸው ታውቋል::

1ኛ ኮሎኔል ተፈራው ደሳለኝ
2ኛ ኮሎኔል ጥግነህ አሳፍረው
3ኛ ኮሎኔል ዳርሰማ ፈርዶሴ
4ኛ ኮሎኔል ጊሚራው ወዳጆ
5ኛ ኮሎኔል መሃመድ እንድሪስ አሚር
6ኛ ሌ/ኮሎኔል ግደይ ሰመረ (ግማሽ ኤርትራዊ)
7ኛ ሌ/ኮሎኔል ዘይኑ አቦይውቅሮ
8ኛ ሌ/ኮሎኔል ጅባት ሞጋ
9ኛ ሌ/ኮሎኔል ካሳዬ ሃብታሙ
10ኛ ሌ/ኮሎኔል ሳላይህ ዋለ
11ኛ ሌ/ኮሎኔል ደርሶ ተስፋይ
12ኛ ሌ/ኮሎኔል ገሩ አዘዘኝ
13ኛ ሌ/ኮሎኔል ካህሳይ ንጉሰይ
ሻለቆች
1ኛ ሻለቃ ቃሉ ተሰማ
2ኛ ሻለቃ ዋቅጅራ ዱላ
3ኛ ሻለቃ ማንያዘዋል ደብሩ
4ኛ ሻለቃ ኡስማን ጡሃ ኽሊል(ፌስቡክ በሌላ ስም ሲጠቀም የተያዘ)
5ኛ ሻለቃ አለማው አበበ
6ኛ ሻለቃ ገብሬሉ ለጥአድርጋቸው
7ኛ ሻለቃ ካሳሁን በድሉ
8ኛ ሻለቃ የማነ ገረዝጊ
ሻምበሎች
1ኛ ሻምበል ሰማው ድንግሉ
2ኛ ሻምበል ተስፋዬ ቤተማርያም(ባቡሩ)
3ኛ ሻምበል ሁሴን አባድር
4ኛ ሻምበል ጉኡሽ ኪዳኔ
5ኛ ሻምበል ሓዲስ አረጋይ
መቶ አለቆች
1ኛ መቶ አለቃ ከፍያለው ገናነው
2ኛ መቶ አለቃ ጃኮብ ኦጁሉ ቶም
3ኛ መቶ አለቃ ሲሳይ አማረ
4ኛ መቶ አለቃ ድልሰፋ ይርጋ
5ኛ መቶ አለቃ ስሜነህ ታምሩ
6ኛ መቶ አለቃ ጌታነህ ደበላ
7ኛ መቶ አለቃ ገመቹ ዳባ
የተባሉ ወታደራዊ መኮንኖች በወያኔ መንግስት ላይ አሲርዋል በሰራዊቱ መካከል አለመተማመን ፈጥረዋል ወዘተረፈ በሚል ሰበብ በየእዙ ምድር ቤት በሚገኙ እስር ቤቶች ሲሰቃዩ ከርመው ካለምንም ፍርድ እና ሕግ ፊት ሳይቀርቡ በሰሜን እዝ እና በደቡብ ምስራቅ እዝ አከባቢ ያለው የሰላም መደፍረስ እንዲሁም በወታደሩ አከባቢ የሚታየውን ማጉረምረም ተከትሎ እስረኞቹ ወደ አለም በቃኝ መምጣታቸው ታውቋል::
እንደሚታወቀው በወያኔ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ከፍተኛ ሽኩቻ እና አለመተማመን ሲኖር የወያኔ ጉጀሌ አገዛዝም ወታደሮቹ ጦርነት ቢከፈትብኝ ከጠላት ጋር ያብሩብኛል በሚል ከፍተኛ ፍራቻ ስላደረበት በጦሩ ውስጥ አስጊ የተባሉ መኮንኖችን እየለቀመ ማሰር ከጀመረ መቆየቱ ይታወሳል:;ይህም የጅምላ እስር/ግዞት የዚሁ የወያኔ ስጋት አንዱ አካል መሆኑን እማኙ ተናግረዋል:: #ምንሊክሳልሳዊ

No comments:

Post a Comment