Monday, August 24, 2015

ከ4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ አስቸኳይ የገንዘብ እርዳታ ያስፈልጋል ተባለ

ነኅሴ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ 4 ነብ 5 ሚሊዮን ሕዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው መንግስትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አጋር የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

በተያዘው አመት 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ታስቦ የነበረ ቢሆንም፤ የተረጅዎች
ከግምት ውጪ ላሻቀበው የተረጅዎች አሀዝ ብቻ 230 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ 4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ በጋራ መግለጫው ላይ የተመለከተ ሲሆን፤ከዚህ መካከል መንግስት 33 ሚሊዮን ዶላር ያህሉን መመደቡና ቀሪው 200 ሚሊዮን ዶላር በአስቸክይ ከውጭ ለጋሾች የሚጠበቅ መሆኑ ተገልጿል።
2015 ከገባ አንስቶ እስካሁን ድረስ 386 ሚሊዮን ዶላር ተመድቦ እርዳታ ሲሰጥ መቆየቱ በመግለጫው ተጠቅሷል።
የተመድ የስብዊ እርዳታ ሃላፊ ዴቪድ ዴል ኮንቴ ፣ የኢትዮጵያ ሚቲሪዮሎጂ ድርጅት የበልግን ዝናብ አስመልክቶ ከተነበየው በጣም የከፋ የዝናብ እጥረት በበልግ ወቅት ተከሰቷል ብለዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ ፤ ትርፍ አምራች የነበሩት እንደ አርሲና ምእራብ አርሲ የመሳሰሉ አካባቢዎች ሳይቀሩ አሁን እርዳታን ይሻሉ።
እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ወረዳዎች ቁጥር ከ49 ወደ 97 ከፍ ማለቱ፤ እንዲሁም አሣሳቢ ሁኔታ ላይ የደረሱና አስቸኳይ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ህጻናት አሀዝም በከፍተኛ ሁኔታ ማሻቀቡ ተገልጿል።
-በኢትዮጵያ የዩኒሴፍ ተወካይ ሚስ ጁሊያን ሜልሶክ- ለጋሽ ሀገሮች እስካሁን በጥሩ ሁኔታ እርዳታ ሲሰጡ መቆየታቸውን በማውሳት- አሁን ያለው ሁኔታ እጅግ የከፋ በመሆኑ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ተማጽነዋል።

No comments:

Post a Comment