Tuesday, November 17, 2015

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ለሶማሊያ ከወታደራዊ ይልቅ ፖለቲካዊ መፍትሔ ያስፈልጋታል አሉ

ኀዳር ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ማህሙድ በአገራቸው ላለፉት አስር ዓመታት ለተንሰራፋው የአልቃይዳና የአልሸባብ ጥቃቶች እልባት ሊገኝለት የሚችለው ፖለቲካዊ መግባባቶችን በመፍጠር ካልሆነ በስተቀር በወታደራዊ የኃይል ጥቃቶች ብቻ ዘላቂና አስተማማኝ የሆነ ሰላም ማስፈን እንደማይቻል አበክረው ተናግረዋል።

በአንድ ነገር ግን እርግጠኛ ነኝ ፣በበርሜል እየሞላን ጥይቶችን እና መሳሪያዎችን ስላዘነብን ብቻ አልሸባብን አናጠፋውም።የእርቅና የምህረት መንገዱን ሁሌም መፈለግ ያሻናል።አሁንም በሽምግልና መንገድ መፍትሔ መፈለጉን እየቀጠልንበት ነው ብለዋል ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ማህሙድ።
እንደ አውሮፓዊያን ዘመን አቆጣጠር ከ2007 ዓ.ም ጀምሮ ከአስር አገሮች የተውጣጡ የአፍሪካ የሰላም አስከባሪ ጦር ወታደሮች በሶማሊያ ቢሰፍሩም ፣ በአገሪቱ ዘላቂ የሆነ ሰላም ማስፈን ግን አልቻሉም። በቅርቡ ከዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ ወጣ ብሎ በደቡባዊ ሶሊያ ጃናሌ ግዛት 80 የሚሆኑ የሰላም አስከባሪ ጦር አባላት መገደላቸውን ብሉንበርግ ዘግቧል

No comments:

Post a Comment