Friday, November 27, 2015

105 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ታንዛኒያ ውስጥ ተያዙ

 ኢሳት ዜና :-በሕገወጥ መንገድ ወደ ታንዛኒያ ግዛት ገብተዋል ተብለው የተጠረጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በዋና ከተማዋ ዳሬሰላም ውስጥ መያዛቸውን የከተማዋ የፓሊስ አዛዥ ኮማንደር ሱሌይማን ኮቫ ገልጸዋል።

አዛዡ ቁጥራቸው 105 የሚሆኑ ያሉዋቸውን ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በዳሬሰላም በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ተደብቀው መያቻውን ገልጸዋል። ስደተኞቹን ጨምሮ ሕገወጥ የሰው ዝውውር ሥራ ይሰራል የተባለው የ25 ዓመቱ ሩዋንዳዊ ዜጋም ተይዟል።
በስደተኞች ላይ የሚደረገው ምርመራ ሲጠናቀቅ፣ ስደተኞቹ በሕጋዊ መንገድ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ሲሉ አዛዡ አክለዋል።

No comments:

Post a Comment