Thursday, November 19, 2015

በሰሜን ሸዋ 23 እስረኞች አመለጡ

ኀዳር ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ማክሰኞ ሸዋ ሮቢት በቀወት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የነበሩ እስረኞች በሙሉ ያመለጡ ሲሆን፣ እስረኞቹ እስካሁን አልተያዙም። አብዛኞቹ እስረኞች በህገወጥ መንገድ ትነግዳላችሁ ተብለው የተያዙ ነበሩ። እስረኞቹ ሌሊት ላይ የጭቃ ቤቱን ግድግዳ በውሃ አርሰው ከቀደዱት በሁዋላ ሁሉም በአንድ ላይ አምልጠዋል።

ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ እስረኞችን ለመያዝ ፍተሻ በመካሄድ ነው። የወረዳው ነዋሪዎች እስረኞችን አምጡ በማለት እየተሰቃዩ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment