Thursday, November 26, 2015

ለብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል 200 ሚሊዮን ብር ተመደበ

 ኢሳት ዜና :-ህገመንግስቱ የጸደቀበት በተለምዶ የብሄር ብሄረሰቦች በአል ህዳር 29 ቀን በጋምቤላ ክልል የሚከበር ሲሆን ፣ ለበአሉ ድምቀት በጋምቤላ ስታዲየም ተገንብቷል። ከ5 ሺ በላይ እንግዶችን ለማስተናገድ የማሰልጠኛ ተቁዋማት የመማሪያ ክፍሎችን ጭምር ወደ ምኝታ ክፍሎች ለመቀየር ታስቦአል።

በፈዴሬሽን ም/ቤት በኩል በየአመቱ ከ200 ሚሊየን ብር በላይ የሚወጣበት ይህ በአል ፣ዘንድሮ ከ15 ሚሊየን በላይ ወገኖች በድርቅ ችግር ውስጥ በሚማቅቁበት ወቅት ይከበራል።

No comments:

Post a Comment