Monday, November 16, 2015

የጎንደር-ደልጊ ነዋሪዎች የሆኑ ከ10 በላይ ሰላማዊ ሰዎች "ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ግንኙነት አላችሁ" በሚል ከጥርጣሬ ያላለፈ ሰበብ ብቻ በህወሓት አገዛዝ ደህንነቶችና የታጠቁ ቡድኖች ታፍነው ተወሰዱ፡፡

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)

የጎንደር-ደልጊ ነዋሪዎች የሆኑ ከ10 በላይ ሰላማዊ ሰዎች "ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ግንኙነት አላችሁ" በሚል ከጥርጣሬ ያላለፈ ሰበብ ብቻ በህወሓት አገዛዝ ደህንነቶችና የታጠቁ ቡድኖች ታፍነው ተወሰዱ፡፡

በህወሓት አገዛዝ ደህንነቶችና የታጠቁ ቡድኖች ቅዳሜ ዕለት ከየመኖሪያ ቤታቸው እየታፈኑ ከተወሰዱት ከ10 በላይ የሚሆኑ የደልጊ ሰላማዊ ነዋሪዎች መካከል፦
•አቶ አሰፋ ገዳሙ
•ወጣት አዲሱ አያሌው
•አቹ ወርቁ
•ሙሉጌታ ክፍሌ 
•ያሃቤ... የተባሉት ይገኙበታል፡፡

በተጨማሪም "ልጅህ ወደ ኤርትራ በመሄድ አርበኞች ግንቦት ሰባትን በአካል ተቀላቅሏል" በሚል ምክንያት አቶ ሙሌ አላምረው የተባሉትን የህወሓት ሰዎች በቁጥጥር ስር ሊያውሏቸው ሲሞክሩ አምልጠው ለመሰወር እንደቻሉ ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡

No comments:

Post a Comment