Thursday, November 26, 2015

የአፍሪካ የሰላምና የደህንነት ጉባኤ በድርቅ የተጎዱ አገሮች እንዲረዱ ጠየቀ

 ኢሳት ዜና :-በደቡብ የአፍሪካ አገራት በቦትስዋና፣ ሌሶቶ፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ሞዛምቢክ፣ ደቡብ አፍሪካና ዝምባብዌ ከምስራቅ አፍሪካ ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ሶማሊያን እንዲሁም በምዕራብ አፍሪካ አገራት የአየር መዛባቱ በሚፈጥረው ድርቅ ሳቢያ የምግብ እጥረትና የሰብዓዊ ቀውስና ግጭቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ ምክር ቤቱ ጠቅሷል። ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ እነዚህ አገራት አስከፊ ቀውስ ውስጥ ከመግባታቸው አስቀድሞ አፋጣኝ የሆነ የሰብዓዊ እርዳታውን መለገስ እንዳለበት በአጽኖት አሳስቧዋል።

በተጨማሪም የዓለም የምግብ ድርጅት FAO ድርቁን ተከትሎ የምግብ ዋጋ መናር እንደሚከሰት፣ በተለይ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በድርቁ ተጠቂ ከሆኑት አገራት ቀዳሚዋ በመሆኑዋ እርዳታ እንደሚያሻት ገልጿል።

No comments:

Post a Comment