Wednesday, January 7, 2015

ኮማንደር ቢኒያም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን በድቅድቅ ጨለማ ብርድ ላይ እያስተኛው በማሰቃየት ላይ ነው

ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ማን እንደሚመራት በማይታወቅባት ሁኔታ አንድ ደህንነት ወይም ወታደር የፈለገውን የማዘዝ ስልጣን ያለው ሲሆን እንገዛለታለን የሚሉትን ህገመንግስት ወደ ጎን በመተው የፈለጋቸውን እርምጃ እየወሰዱ በመሆኑ በስር ዓቱ ውስጥ ያለውን አለመደማመጥ ያሳያል የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞች በቅርቡ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን በአንድ ደህንነት ት ዕዛዝ ብቻ ለ3 ሳምንታት ከሃገር እንዳይወጣ ፓስፖርቱን መቀማቱን ያስታውሳሉ።

በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ በዝዋይ እስር ቤት እየደረሰ ያለው ስቃይ ኮማንደር ቢኒያም በሚባል አዛዥ ሲሆን ተመስገንን በአንድ ምሽት ከ5 ጊዜ በላይ በድቅድቅ ለሊት በማስወጣት ብርድ ላይ እንደሚያስተኙት ከስፍራው የደረሰው መርጃ ያጋልጣል።

በተለይ ተመስገን ደሳለኝ “የመንግስት ገመና” በሚል ከእስር ቤት ከፃፈ በኋላ ደህነነቶች እና ይኸው ኮማንደር ቢኒያም የሚባል አዛዥ የእንግልሃለን ሬሳህን እዚህ ብንጠለው ዞር ብሎ የሚያይህ የለም በሚል እንደሚያስፈራሩት የጠቆሙት የዜና ምንጮቻችን ድብደባ እንደተፈጸመበትም ታውቋል።

ኢትዮጵያ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ግለሰቦች የሚያዙባት፤ በአንድ ግለሰብ ትዕዛዝም ሕይወት የሚጠፋባትና የሚበላሽባት ሃገር እየሆነች መምጣቱ የስርዓቱን ደጋፊዎች ሳይቀር እያስቆጣ እንደሚገኝ ከተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።


No comments:

Post a Comment