Friday, January 23, 2015

“ለልጆቼ የማይሆን ተስፋ አልነግራቸውም” የነፃነቱ ታጋይ አንዳርጋቸው ፅጌ


ከልጅ አያሌው

ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ትግል እስከወዲያኛው ከዳር ለማድረስ ቆርጦ ልጆቼን ቤተሰቦቼን ሳይል ከራሱ በላይ በሀገሩ ፍቅር ተበልጦ የተሻለ ነው የሚለውን፣ አማራጭ የሌለውን፣ የኤርትራን ጫካ መርጦ የማይቻል የሚመስለውን ችሎ ብዙዎች ፈቀቅ ማድረግ ያቃታቸውን የመተባበር የመያያዝ በአንድ ገብቶ ለአንድ አላማ የመታገልና ኢትዮጵያን እንደቀደመው ታላቅ ሀገር የማድረግ ውጥን የተሻለና የሚያግባባ ሀሳብ በመሸከፍ ከሚመራው ንቅናቄ ከግንቦት 7 ጋር እጅግ እውነት የማይመስሉ ድንቅ ስራዋችን በመስራት ጠማማውን በማቅናት ኮረብታውን በመደልደል አንድ መሆን ሳይችሉ ለአመታት ሲኳትኑ የነበሩትን በኢትዮጵያዊነት እንዲተሳሰሩ በማድረግ ፍቅር የሰራ ትልቁን መሰረት የጣለ ምርጥ የኢትዮጵ የቁርጥ ልጅ አንዳርጋቸው ፅጌ።

ዛሬ እሱ በማረፍያው ሰዓት አግባብ ባልሆነ መንገድ ከአውሬዋች እጅ ወድቆ ይህን መልዕክት አስተላልፏል። ለልጆቼ የማይሆን ተስፋ አልነግራቸውም።


ይሄ መልዕክት ኢትዮጵያን ለሚወዱ ሁሉ እጅግ የሚያም ነው ምክንያቱም እየከፈለ ያለው መሰዋት ለኛ ለኢትዮጵያኖች ስለሆነ።

አንዳርጋቸውን ከግንቦት 7፣ ግንቦት 7ን ከአንዳርጋቸው መነጠሉ የማይሞከር ነው ምክንያቱም ሀቁ የሚነግረን እሱና እሱን ከሚመስሉ ወንድሞች ጋር ታላቅ የሆነ ኢትዮጵያን የማዳን ራዕይ ሰንቀው በግድ ሳይሆን በፍቅር ተሳስረው አንዳይነት አላማ አንግበው ማድረግ ከሚችሉት በላይ ሌተቀን ደከመን ሰለቸን ሳይሉ ከማንም በላይ የየግል ህይወታቸውን መኖር እየቻሉ ያለመታከት ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ታላቅ ለማድረግ የተሰለፉለት አላማ መሆኑ በግልፅ የሚታይ ሀቅ ስለሆነ።

ታድያ አንዳንዶች የኢትዮጵያዊነትን ካባ የለበሱ የሚመስሉ እየደረሰበት ያለውን ስቃይ በመኮነን ድንቅ ሰው ታላቅ ሰው መሆኑን አክለውበት ጀግናችን ነው ብለው ሲያበቁ አንዳርጋቸውና ንቅናቄው አምነውበት: በአሁን ሰአት ካለው የሀገራችን አንዲሁም የጎረቤት ሀገራት ሁኔታን በማጤን አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን በመረዳት በትግል የዘረጉትን ገመድ በጥሶ ለመጣል ያስችለናል የሚሉትን የሰነፍ ስንቅ በመሰነቅ እየተሄደበት ያለውን መልካም መንገድ ፈንጂ የተጠመደበት በማስመሰል አንዳንዴ በዛበኩል ትግል ለሚያደርጉት ከልብ ያዘኑ በመምሰል አልሆን ሲላቸው ደግሞ በዛ በኩል የሚደረግ ጉዞ ለሀገር አደጋ አለው በማለት ነጋ ጠባ ያለ ህፍረት መከራቸውን ሲያዩ ስምለከት ከሚቆረጥላቸው አበል ጥቂቱን እንኳን ደጉሜ ነፃ ሰው ባደርጋቸው እልና ፀረ ትግልና ፀረ ነፃነት መሆናቸው ሲታወሰኝ ከእንዲህ አይነቱ ሱስና አመል ማላቀቁ ከአቅሜ በላይ መሆኑን ሳውቀው አንድላይ ደባልቆ ማሸቱን እመርጥና እተወዋለው።

በነገራችን ላይ ይሄ አባዜ በነዚህ እኩይ ተግባር ባላቸው ጥቂት ሰዋች ብቻም አይቀነቀንም ይልቁንም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊነት ያለምንም ማወላወል አንገታቸውን ሊሰጡ በሚችሉ ሰዋችም ወቅት አየጠበቀ እንደሚያጓራ ዛር ሲያወራጫቸው ይስተውላል ታድያ የችግሩን መንስኤ ሳጠናው ፍቅር ሆኖ አግኝቸዋለው ፍቅር ደሞ እዚ ውስጥ ምን ከተተው ትሉኝ ይሆናል? ይሄኛው ወዲህ ነው አትጣበቅ እንጂ አንዴ ከተጣበክ አትታጠር እንጂ አንዴ አጥር ከሰራህ ማየትም መስማትም የምትፈልገው ያፈቀርከውን ብቻ ነው ወገኖቼ በድርጅት ፍቅር እንዳታብዱ የትም ስለማያደርስ :አንዴ ግን ከተለከፋቹ የተሰራው እናንተ ካልሰራችሁት የተጀመረው እናንተ ካልጀመራችሁት የታሰበው መልካም ሀሳብ ከናንተ ቀድሞ ካልፈለቀ ገደል አፋፍ ላይ ነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ተይዛቹ እንኳን የማዳን እጅ ቢዘረጋ አይናቹ ማየት የለመደውና የምታፈቅሩት እጅ አለመሆኑን ስታውቁ መዳንን ትፀየፉታላቹ ገደል መግባቱን ትመርጣላቹ ስለዚ እውነት ሀገራችንን ማዳን ከፈለግን ሜዳው ሰፊ ነውና እኔ ካልባረኩት የሚለውን ፍሬ ከርስኪ ትተን ሌላውን ከመጎተት የተሻለ የምንለውን ሜዳ በመምረጥ ለሀገራችን አለኝታ እንሁን።

ሌላኛው ደግሞ እጅና እግሩ ተጠፍንጎ የታሰረበት ይመስል ከማሳየት ይልቅ ጥግ ይዞ የታላቹ፣ የት ገባቹ፣ ጦርነት የሆሊውድን ፊልም አይነት እየመሰው በከንቱ ምኞት መሬት ላይ ወርዶ ህይወቱን ለሀገሩ አሳልፎ ለመስጠት ነጋ ጠባ መከራውን የሚያየውን የነፃነቱን አርበኛ ከሶፋው ላይ ተደላድሎ ተቀምጦ እግሩን ጠረጴዛ ላይ ሰቅሎ ቢራውን እየተጎነጨ ከኮንፒውተር ጀርባ ሆኖ ሲከተክተው ይውላል ደሞ እፍረትም የለውም ትግላችን፣ የኛ ትግል፣ እያለ እየደጋገመ ሲናገር ይደመጣል እኔ ግን እላለው: መጀመርያ እጃችንን ከኪሳችን ታግለን ነፃ እናውጣው። ሀገራችንን ለማዳን የሚደረገውን ትግል ለመደገፍ ሰበብ አንደርድር።

በመጨረሻም አንድ ወዳጄ ለጨዋታ ባወረዳት ቅኔ ለጠቅ አድርጌም የኔንም የመልስ ምት አክዬ ልደምድም፣

እኔ እናገራለሁ ቆሜ ከፊታቹ
ጠሀይ አልወጣ አለች ከሰሜን ወርዳቹ

መልስ

የጠሀይን መውጫ ልብህ እያወቀው
ብላ ተኛ ሆነህ የቆረጠውን ሰው
በየትኛው ወኔነው የምትጠይቀው

ቅኔው የወዳጄ ሆና እሱ ባያቀነቅናትም ይህቺን ዘፈን ብዙዋች ይዘፍኗታል እስኪ ካስተማረች በተን ላድርጋት፣

ለመሆኑ የጠሀይ መውጫ በሰሜን ሆነ እንዴ? የኔ ጥያቄ ነው ጠሀይ በምስራቅ ወጥታ በምዕራብ ትጠልቃለች የወዳጄ ጠሀይ ግን :ከወትሮው ለየት አለችብኘ ለነገሩ ራቅ አድርገው ካሰቡት ጠሀይ በእድሜም የጠገበች እንደመሆኗ ተወዳጅነቷ ዋዛ እንደማይሆን አልጠራጠርም።

ወዳጄም የመናፈቅ ብዛት ሳያናግረው አልቀረም ስለዚህ ወንድሜ ጠሀይን እኛ አላገድናትም መውጫዋም በምስራቅ ነው እኛ ግን መንደርደርያ የለንምና በሰሜን ከተናል ባይሆን ባገኘናት እድል ተጠቅመን ከሰሜን ተነስተን የጠፋችብህን ጠሀይ ከዚህ ሰፈር ሳይሆን ሰፈሯ ድረስ በመምጣት ብቅ እንድትል ማረጋችን እንደማይቀር ላረጋግጥልህ እወዳለሁ የምትቸኩል ትዕግስት የሌለህ ከሆነ ግን ጠሀይ ብቅ እንድትል ስትፈልግ በደቡብ፣ ስትፈልግ በምዕራብ፣ የሚያስጠጋህ ከገኘህ በዛ በኩል ሞክር።

ምስራቁ ቅርብ ነውና ባትደላደል እንኳን ጫፍ የሚያስይዝህ ካገኘህ ያው መደወል አትወድም ምልክት አድርግልኝ ያለህበት ድረስ መጥቼ እቀላቀልሀለው እውነቴነው የምልህ ጠሀይቱ እናቴ ጋር እስካደረሰኘ ድረስ የማልቆፍረው ገድጓድ የማልወጣበት ተራራ፣ የማልሞክረው አቋራጭ አይኖርም።

በሰሜን የከተቱት ብዙ ጊዜ ተጠይቀው ሲመልሱት ካደመጥኩት ቅንጭብ የተወሰደ ነው በሚል ይያዝልኝ።

ስለዚ መጠላለፉን ትተን የምንችለውን እናድርግ ያ ከሆነ ትግሉን መሬት ላይ አውርዶ እየሰራ ያለውም በአየር ላይ ያለውም በመጨረሻዋ ቀን የነፃነቷ ጠሀይ በሀገራችን ስትወጣ እኩል ይቋደሳሉና።

ይህንን ለመፃፍ ያነሳሳኝ “ለልጆቼ የማይሆን ተስፋ አልነግራቸውም” የሚለው የጀግናው ታጋይ የአንዳርጋቸው ንግግር መሆኑነ አሰምርበታለሁ።

በዘገየን መጠን የምናጣው ይበዛልና ባለመጠላለፍ ወደፊት እንሂድ፣ እኔ የሁሉም ነኝ የተሻለ አማራጭ ያለው ይገዛኛል።

ኢትዮጵያ ለዘላላም በክብር ትኑር!

እናቸንፋለን!

ልጅ አያሌው


No comments:

Post a Comment