Friday, January 2, 2015

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይግባኝ ለታህሳስ 30 ተቀጠረ * ዝዋይ እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ችሎቱን ተከታትሏል

(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ያስገባው የይግባኝ ጥያቄን ለመስመት ስድስት ኪሎ የሚገኘው ፍርድ ቤት ተሰይሞ የነበረ ሲሆን ጉዳዩን ተመስገን እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ተከታትሏል::

ከ’ፍሪ ተመስገን ደሳለኝ” የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ዛሬ ታህሳስ 23/2007 ጠቅላይ ፍረድቤት በዋለው ችሎት የጋዜጠኝ ተመስገን ደሳለኝን ይግባኝ ከሰማ በኋላ ጉዳዩ ለይግባኝ ያስቀርባል አያስቀርብም የሚለውን ለመወሰን ለታህሳስ 30/2007 ዓ.ም ቀጥሮ ሰቷል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ችሎቱን የተከታተለው ዝዋይ እስር ቤት ሆኖ በፕላዝማ ነው::


No comments:

Post a Comment