Sunday, January 11, 2015

በቂሊንጦ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን አስታወቁ

በቂሊንጦ ከሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች መሃል የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው እና የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ለአዲሱ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ በላይ ፍቃዱ ድጋፋቸውን መስጠታቸውን ተከትሎ በወህኒ ቤት ውስጥ ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

አመራሮቹ ስቃይ እየደረሰባቸው የሚገኘው ለአቶ በላይ ፍቃዱ እውቅና ሰተው በሌላ በኩል በአንድነት ስም በተጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለተመረጡት የፓርቲው ሰዎች እውቅና መንፈጋቸውን ተከትሎ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአንድነት ፓርቲ አመራር የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከሃምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡


No comments:

Post a Comment