Thursday, January 8, 2015

አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል – አቶ ኪዳኔ አመነ – የመድረክ ወጣት አመራር

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በተመለከተ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን የማፅዳት ሃላፊነት ከተወጣ በኋላ ገዢው ፓርቲ ጥርሱን የነከሰበት ይመስላል፡፡ ብዙ ፈተና እየገጠመው ነው፡፡ በምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እስከማድረግም ደርሰዋል፡፡በኔ እምነት አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ብዙ ርቀት የሄደ ይመስለኛል፡፡ ትእግስታቸው አደንቃለሁ፡፡ ፓርቲው በውስጡ ከጥቂቶች በቀር በዙዎቹ ቁምነገር የሚያስቡ የምናከብራቸውና የምንወዳቸው ጥሩ ሰዎች አሉት፡፡ ትርጉም ያለው የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ ጥቂት ፓርቲዎች አንድነት አንዱ ነው፡፡ እናም በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ና እውነተኛ ፍትህ ለማምጣት የአንድነት መኖር ከፍተኛ ትርጉም አለው፡፡ ፓርቲው የአንድነት ፓርቲ አባላትና የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሣይሆን የራሳችን አቋምና መስመር ይዘን በሌላ ፓርቲ ያለን ሰዎች እንኳ አንድነት እንዲኖር አጥብቀን እንፈልጋለን፡፡ ወደፊት አንድነትም እኛም ቤታችን እያፅዳን መንገድ ላይ መገናኘት አለብን፡፡

ያኔ ብቻ ነው ኢትዮጵያን የምናድናት፡፡ እንዳንራመድ ቀይዶ የያዘን ገመድ እየበጣጠስን፤ ፀረ-ለውጥና አድሃሪ አቋምን እየመከትንና እያፀዳን የዴሞክራሲ እና የሉዓላዊነት ፍለጋው ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡

አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል ፡፡ አንድነቶች አሁን ነው የፖለቲካ ፅናታቸው በጥበብ ማሳየት ያለባቸው፡፡ ወንድሞቻችን በርቱ!!!


No comments:

Post a Comment