Monday, May 9, 2016

አቶ ዳንኤል ሺበሺና የሽዋስ አሰፋ ተፈቱ


ሚያዚያ ፩(ግንቦት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ምርጫ 2007ትን ተከትሎ በሽብርተኝነት የተከሰሱት የቀድሞው የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሃላፊና የደቡብ ተወካይ አቶ ዳንኤል ሽበሺ እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ም/ል ሰብሳቢ አቶ የሺዋስ አሰፋ የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ተፈተዋል።
አቶ ዳንኤልና አቶ የሽዋስ ነሃሴ 14 ቀን 2007 ዓ•ም ፍርድ ቤት ነጻ ቢላቸውም፣ በችሎት መድፈር በተላለፈባቸው ውሳኔ እስከዛሬ በእስር እንዲቆዩ ተደርጓል። በተመሳሳይ ወንጀል የተከሰው አቶ አብርሃ ደስታም ከሁለት ወራት በሁዋላ ይፈታል ተብሎ ይጠበቃል።

No comments:

Post a Comment