Friday, May 13, 2016

በደንቢያ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ መምህራን አድማ አደረጉ

ግንቦት ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መምህራኑ ዛሬ ከጠዋቱ 4 ሰአት ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ ያደርጉ ሲሆን፣ መንግስትን የሚያውግዙ መፈክሮችን ሲያሰሙ እንደነበር ምንጮች ገልጸዋል።
አድማውን ትከትሎ ትምህርት በመቁዋርጡ ተማሪዎች ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ ተደርጎአል።
ባድማው የተሳትፉ መምህራንን ለማነጋገር ሙከራ ብናደርግም፣ ከሰአት በሁዋላ ወደ ስብሰባ በመግባታቸው ሳይሳካልን ቀርቶአል። መምህራኑ መብታችን ሳይከብር ስራ አንጀምርም ማለታቸውን ተማሪዎች ለኢሳት ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment