Tuesday, May 17, 2016

አዲስ አጭር መረጃ ስለታላቁ የነጻነት ታጋይ አንዳርጋቸዉ ጽጌ!!

ከልዑል ዓለሜ
በመላዉ ኢትዮጵያዊያን ልቦና ዉስጥ ሰርጾ መግባት የቻለና የማይበርድ የትግል ምእራፍን በመንደፍ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊያን ነጻነትን የቀለመ አባት ነዉ ! እ.ኤ.አ በግንቦት ወር /2014 የየመን ዋና ከተማ ሰናአ ላይ ተሰወረ! የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን ለወንበሬ ያሰጋኛል ብሎ በጠላትነት የተነሳበት የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ ክቡር አንዳርጋቸዉ ጽጌ በግፍ ለወንጀለኛዉ የወያኔ ቡድን ተላልፈዉ ተሰጡ!

ነጻነት ላያንቀላፋና ነጻነት ላይታሰር አንድነትና ኢትዮጵያዊነትን በጫንቃዉ ተሸክሞ በማረፊያዉ ወቅትና ሰአት የጎረመሰዉ አባት አንዳርጋቸዉ ጽጌ ብዙሃንን አፍርቷል!! ዛሬ የፍሬዉ ትሩፋቶች አደራቸዉን ተቀብለዉ ሐገራቸዉንና ትዉልዳቸዉን ለመታደግ ዳር በደረሱበት ወቅት ወያኔያዉያን ግን ታላቁን አባት ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ላይ ይገኛሉ! ከሰሞኑ በደረሰን መረጃ መሰረት የተከበሩት የነጻነት አባት ክቡር አቶ አንዳርጋቸዉ ጽጌ የፌደራል ፖሊስ ህንጻ ስር ምድር ቤት ዉስጥ ( underground ) ክፍል ዉስጥ መወሰዳቸዉን የሚያረጋግጡ ሲሆን የብሔራዊ መረጃ ምንጮቻችን በበኩላቸዉ ሌሎች ተጨማሪ ግለሰቦች በዚያዉ በፌደራል ፖሊስ የምድር ቤት ብቸኛ ክፍል ዉስጥ ከታላቁ የነጻነት አባት ጋር እንደሚገኙ ፍንጭ ሰጥተዋል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

No comments:

Post a Comment