Wednesday, May 25, 2016

የኢህአዴግ መንግስት ወታደራዊ ሃይሉን ለማጠናከር የጦር መሳሪያዎችን በብዛት እየሸመተ ነው

ግንቦት ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመከላከያ ሰነዶች እንደሚያመለክቱት ካለፉት 2 አመታት ጀምሮ የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ የሆነ ወጪ በማውጣት የጦር መሳሪያዎችን እየገዛ ሲሆን፣ የጦር መሳሪያ ባለሙያዎችንም ወደ ቻይናና ሌሎች የምስራቅ አውሮፓ አገራት በመላክ እያሰለጠ ነው።

ሰነዶቹ እንደሚያስረዱት በሁለት አመታት ውስጥ መንግስት ለታንክ መግዢያ ብቻ ከ684ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያደረገ ሲሆን፣ ለመድፎች 896 ሚሊዮን ብር፣ ለተሽከርካሪዎች ፣ ለተለያዩ ጠመንጃዎች፣ ለቦንቦችና ለመሳሰሉት ወታደራዊ ቁሳቁሶች ደግሞ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርጓል። ይህ አሃዝ ከመስከረም 11፣ 2005 ዓም እስከ 2007 ዓም ያለውን ጊዜ ብቻ የሚመለከት ነው።
በብዛት የገቡት የጦር መሳሪያዎች ሩስያ ሰራሽ የሆኑ ቲ- 172 የሚባሉ ታንኮችና 122 ሚሊሜትር መድፎች ናቸው።

No comments:

Post a Comment