Monday, May 16, 2016

በአማራ ክልል የሳንቲም እጥረት ተፈጠረ

ግንቦት ፲፩ (አሥራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የክልሉ ዘጋቢያችን እንደገለጸው በተለይ በክልሉ ዋና ከተማ ባህርዳር የአንድ ብር ሳንቲም እጥረት በመከሰቱ ታክሲዎች ፣ ደንበኞቻቸውን ከማሳፈራቸው በፊት ጥያቄያቸው “ ዝርዝር ሳንቲም ይዘሃል ?” የሚል ሆኗል። ለተፈጠረው የሳንቲም እጥረት ትክክለኛ ምክንያቱን ለማወቅ ባይቻልም፣ ባለፈው አመት መጋቢት ወር ድምጻችን ይሰማ የጠራው የሳንቲም መሰብሰብ ሰላማዊ የተቃውሞ ማእቀብ ውጤት ሊሆን እንደሚችል አንዳንድ ነዋሪዎች አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

No comments:

Post a Comment