Friday, September 18, 2015

በኩዌት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ ላይ የሞት ፍርድ ውሳኔው ጸናባት

መስከረም ፯ (ሳባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ዓመት በኩዌት ሱላቢካት ከተማ ውስጥ የአሰሪዋን ልጅ የ19 ዓመቷን ወጣት ሲሃም ማህሙድ በስለት በመግደል ወንጀል ተከሳ የነበረችው የ22 ዓመቷ ኢትዮጵያዊት ወጣት ራቢያ ማህሙድ ላይ የተላለፈው የሞት ፍርድ ውሳኔ መፅናቱን የአገሪቱ ፍርድ ቤት አስታውቋል።

ግድያውን ለመፈጸም ያበቃት ሟቿ መኝታ ክፍልዋ በተደጋጋሚ ጊዜ በመምጣት በር በመዝጋት ጥቃት የምትፈጽምባት መሆኑንና ይህ ተደጋጋሚ ጥቃት በፈጠረባት ስሜት የተነሳ በስለት ወግታ መግደሏን ለፖሊስ ቃሏን ሰጥታለች።
ሟቿ የቀድሞ የኩዌት ብሔራዊ እግርኳስ ቡድን ተጫዋችና የአገሪቱ የወጣቶችና የስፖርት ምክትል ኃላፊ ማህሙድ ፍሌዝ ልጅ ስትሆን፣ በወቅቱ ኢትዮጵያዊያን የቤት ሰራተኞች ወደ ኩዌት እንዳይገቡ እገዳ እንዲጣል ሲጠይቅ ነበር።
የኢህአዴግ መንግስት የሞት ፍርድ ለተፈረደባት ኢትዮጵያዊት ምንም ዓይነት የህግ እገዛ አላደረገላትም።

No comments:

Post a Comment