Tuesday, September 15, 2015

ሰበር ዘና ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ የሚመራዉ ወንጀለኛዉ ቡድን በአለም ዙሪያ የሚገኙ ኤርትራዉያንን ሊሰበስብ ነዉ።

ይህዉ የኢትዮጵያና የኢትያዊያን ጠላት ወያኔ በተለይም ከፍተኛ የሆኑ የአርበኞች ግንቦት 7 ደጋፊዎችና አባላት አሉበት በሚባሉ የአለም ሐገራት የሚገኙ ተቃዋሚ ኤርትራዊያንን ኢላማ ያደረገ ሚስጢራዊ ስብሰባ ለማድረግ መወሰኑን እንዲሁም ከብሐራዊ መረጃ ለየሐገራቱ የኢትዮጵያ ኢንባስሲ ሰራተኞች ትእዛዝ መተላለፉን የደረሰን መረጃ አመለከተ።

17/09/2015 በደቡብ አፍሪካ የሚጀመረዉ ይህዉ ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ በኖርዌይና ስዊድን እንደሚቀጥል ታዉቋል። በመሆኑም ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ ለነዚሁ ኤርትራዊያን ልብ ማማለያ ይሆን ዘንድ ወደ ሐገር ቤት የሚገቡበት ፓስፖርት (travel document) ፣ የገንዘብ ድጎማ፣ የመሬት አቅርቦት እና የንግድ ፈቃድ (work permit) ፣ የአስመጪ እና ላኪ ፍቃድና እገዛ (import and export license) የሚሰጥ ሲሆን በተለየ መልኩ ዋና ትኩረቱ በኤርትራ መንግስት ላይ አለም አቀፍ ተቃዉሞ ለማስነሳት መሆኑ ታዉቋል

ወያኔ ኤርትራዊያኑ ለአርበኞች ግንቦት 7 ድጋፍ የሚሰጡ ኢትዮጵያዊያን ግለሰቦች የኤርትራን መንግስት እድሜ በማራዘም እያገዙት ነዉ በሚል አጀንዳ ተቃዋሚያኑ ከሀገራችን ይዉጡ በማለት ሰልፍ እንዲወጡ ለማነሳሳት እና በኢትዮጵያ የሚኖረዉን የኤርትራ ተቃዋሚ ሐይል እንዲያግዙ ለማድረግ በወያኔ በኩል ተቃዥቷል ይላል መረጃችን።
ወያኔ ተቃዋሚዎቹ እጅግ ሰልጥነዉና በሚገባ ታጥቀዉ ሊፋለሙት በጀመሩበት በዚህ በመጨረሻዉ የመዉደቂያዉ ሰአቱ አለኝ የሚለዉን ተንኮሉና ሴራዉን እያደረገ ቢሆንም ተቃዋሚ ሐይሎቹ እጅግ ከሚገመተዉ በላይ ወደፊት እየገሰገሱበት ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ በሚፈናቀልበትና በረሐብ አለንጋ በሚገረፈበት በዚህ በዘመነ ወያኔ ወቅት ይህዉ ቡድን የሐገራችንን አንጡራ ሐብት ለፖለቲካ ጥቅሙ እያባከነዉና እያፈሰሰዉ ይገኛል ሆኖም አንዳንድ ያነጋገርናቸዉ አርትራዉያን በስፍራዉ በመገኘት ተቃዉሞዋቸዉን እንደሚያሰሙ ለማወቅ ተችሏል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔ ይዉደም!!!

No comments:

Post a Comment