Saturday, September 12, 2015

በጋምቤላ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች የኮሌራ ወረሽኝ ተቀሰቀሰ

ጷግሜን ፭፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በተጠለሉባቸው የስደተኞች መጠለያዎች ውስጥ የተቀሰቀሰው የኮሌራ ወረሽኝ በአጎራባች የደቡብ ሱዳንና የኢትዮጵያ ድንበሮች አካባቢ ስጋት እየፈጠረ ነው።

ይህንን ተላላፊ ገዳይ በሽታ ለመግታት የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅትና ዓለም አቀፉ ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በጥምረት ክትባትና የንጹህ ውሃ አገልግሎት አቅርቦት መስጠት ጀምረዋል።በአስር የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ለሚገኙ መቶ ሰማንያ ሽህ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ክትባት መሰጠቱን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል።

No comments:

Post a Comment