Tuesday, September 29, 2015

ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት ታሰረ

መስከረም ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ችግር በማጋለጥ እንዲሁም የተለያዩ የሰብአዊ ድጋፎችን በማድረግ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት ፣ በየመን የጸጥታ ሃይሎች መታሰሩ ታውቋል።

ጋዜጠኛ ግሩም በምን ምክንያት እንደታሰረ የታወቀ ነገር የለም። ኢሳት ባለቤቱን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካለትም።
በየመን በመካሄድ ላይ ያለውን አስከፊ ጦርነት ተከትሎ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን ግፍ እንዲሁም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ስደተኞችን በሚመለከት የሚያወጣቸውን ዘጋባዎች ተከታትሎ በማጋለጥ በኩል ከፍተኛ ስራ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ጋዜጠኛ ግሩም ከምርጫ 97 ጋር በተያያዘ ተከሶ ፣ ያለፉትን 10 አመታት በየመን በስደት አሳልፏል።

No comments:

Post a Comment