Wednesday, June 27, 2018

አንድ አማራ የአቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ጥሪ ተቀብያለሁ አለ

No automatic alt text available.(ኢሳት ዲሲ–ሰኔ 20/2010)የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በውጭና በሃገር ውስጥ ለሚገኙ በአማራ ስም ለሚንቀሳቀሱ የፖለቲካና የሲቪክ ድርጅቶች ያቀረቡትን ጥሪ እንደሚቀበለው አንድ አማራ የተሰኘው ድርጅት አስታወቀ።
በቅርቡ የተመሰረተውና መቀመጫውን በአሜሪካ ያደረገው አንድ አማራ ፕሬዝዳንት ገዱ አንዳርጋቸው ያቀረቡትን የአብረን እንስራ ጥሪ በቅን ልቦና መቀበሉን አስታውቋል።
ምንም እንኳን የአካሄድ ልዩነቶች ቢኖሩንም ስለሕዝባችን ህልውና አንድ አማራ ከብአዴን ጋር በጋራ ለመስራት ያለውን ዝግጁነት ያረጋግጣል ይላል አንድ አማራ ለኢሳት በላከው መግለጫው።

No comments:

Post a Comment