Tuesday, June 26, 2018

የኤርትራ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ

(ኢሳት ዜና ሰኔ 19 ቀን 2010 ዓ/ም) ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከኤርትራ የመጣውን ልኡካን ቡድን በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው አቀባበል አድርገውለታል፡፡ የኤርትራው ፕሬዝዳንት አማካሪ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ የማነ ገብረዓብ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኦስማን ሳሌህና በአፍሪካ ህብረት የአገሪቱ አምባሳደር የሆኑት አርዓያ ደስታ ከልዑካን ቡድኑ አባላት መካከል ይገኙበታል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከኤርትራ የመጣውን ልኡካን ቡድን በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው አቀባበል አድርገውለታል፡፡ ኤርትራ ጠ/ሚኒስትር አብይ አቅርበውት ለነበረው የሰላም ጥሪ አወንታዊ ምላሽ በሰጠች በአጭር ጊዜ ውስጥ ዲፕሎማቶቿን መላኳ በሁለቱ አገራት መካከል የቆየውን ችግር ለመፍታት ቁርጠኝነት ማሳየቱዋን ታዛቢዎች ይናገራሉ። የልኡካን ቡድኑ ጠ/ሚኒስትር አብይ ኤርትራን እንዲጎበኙ ግብዣ ሊያደርጉ ይችላሉ ሲሉ እነዚህ ወገኖች አክለው ገልጸዋል። በሁለቱ አገራት መካከል የቆየው ችግር ከተፈታ በአካባቢው ዘላቂ ሰላም ለማስፈን እንደሚቻል ይታመናል።

No comments:

Post a Comment