Friday, June 15, 2018

የኢድ አልፈጥር በመላ አገሪቱ እየተከበረ ነው

(ኢሳት ዜና ሰኔ 8 ቀን 2010 ዓ/ም) 1 ሺህ 439ኛው የኢድ አል ፈጥር በአል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስነስርዓቶች በመከበር ላይ ሲሆን ሙስሊም ኢትዮጵያውያውን የተፈናቀሉ እና በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ያሉ ዜጎችን እንዲያስቡ የሃይማኖቱ መሪዎች ጥሪ አቅርበዋል። በዓሉ በአዲስ አበባ ስታዲየም ያለ ጸጥታ ችግር ተከብሯል። በጅጅጋ በአቶ አብዲ አሌ ትዕዛዝ በከተማው ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢድ በአል በአደባባይ አለመከበሩን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በሌሎች ከተሞች ያሉ የክልሉ ተወላጆች ግን ከኢድ በአል በሁዋላ አብዲ ኢሌን የሚያወግዙ መፈክሮች በማሰማት ተቃውሞአቸውን ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment