Monday, June 18, 2018

በለኩ በነበረው ጥቃት ከፍተኛ ውድመት ደረሰ

 (ኢሳት ዜና ሰኔ 11 ቀን 2010 ዓ/ም) ባለፈው ቅዳሜ ከሃዋሳ 25 ኪሜ ርቅት ላይ በምትገኘው ለኩ ከተማ ፣ የአብይ አህመድን አስተዳደር ያልተቀበሉ የደቡብ ክልል መሪዎች እንዳስነሱት በሚነገረው ግጭት በርካታ ጥፋት ደርሷል። የሲዳማ ወጣቶችን በማደራጀት በሌሎች ብሄሮች ላይ ጥቃት እንዲፈጸምባቸው የተደረገ ሲሆን፣ በርካታ የንግድ ቤቶች ወድመዋል። የአካባቢው የፖሊስ ሃይል ድርጊቱን በዝምታ መመልከቱን የአካባቢው ተወላጆች በጽኑ አውግዘዋል። ምንም እንኳ ግጭቱ ትናንትና ዛሬ ጋብ ያለ ቢመስልም፣ አሁንም ውጥረት መኖሩን ያነጋገርናቸው ሰዎች ገልጻዋል።

No comments:

Post a Comment