Thursday, June 21, 2018

የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ገተርስ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በመካከላቸው የነበረውን ውዝግብ ለመፍታት እና ወደ ሰላም ለመምጣት መስማማታቸውን አደነቁ።

(ኢሳት ዜና ሰኔ 14 ቀን 2010 ዓ/ም)ዋና ጸሀፊው የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በመካከላቸውና በአጎራባች ሀገራት ጭምር ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የሚያስችል ስምምነት ለማምጣት እያደረጉ ያለውን ጥረትም አወድሰዋል።. ከዋና ጸሀፊው ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት የወጣው መግለጫ እንደሚለው፣ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ሰላማዊ መንገድ መመለሱ፣ በአጠቃላይ በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሰላም ለማስፈን አስተዋዖው ከፍ ያለ ነው። ሀገራቱ ሰላም ለመፍጠር በሚከተሏቸው ሂደቶች ተመድ አስፈላጊ የሆኑ ድጋፎችን ሁሉ ላማድረግ ዝግጁ መሆኑንም አንቶኒዮ ገተርስ አስታውቀዋል።.

No comments:

Post a Comment