Friday, October 6, 2017

በቆላ ድባ አንድ ወጣት በመከላከያ አባላት ተደብድቦ ተገደለ

በደንቢያ ወረዳ ባርጫ ቀበሌ የተወለደው ወጣት ደመላሽ በመከላከያ አባላት ተይዞ ለሳምንታት ጃንጎ በሚባለው ወታደራዊ ካምጽ ውስጥ ሲደበደብ በመቆየቱ ህይወቱ ማለፉንና የቀብሩ ስነስርዓት ዛሬ መፈጸሙም የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡በርካታ ወጣቶችም እንዲሁ በዚሁ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ታስረው ድብደባ እንደሚፈጸምባቸው ነዋሪዎች ይናገራሉ። በሌላ ዜና ደግሞ በቆላ ድባ ካለፈው አንድ አመት ጀምሮ የስልክ ኔትወርክ ማታ ማታ እየጠፋ ጠዋት ላይ እንደሚለቀቅ ነዋሪዎች አክለው ገልጸዋል። አካባቢው የነጻነት ሃይሎች የሚንቀሳቀሱበት የሚንቀሳቀሱበት ስፍራ መሆኑ ይታወቃል።

No comments:

Post a Comment