Monday, October 2, 2017

በባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 04 የሚገኘው የቴሌ ቢሮ ላይ ፈንጂ ተጠምዶ ተገኘ

(መስከረም 22 ቀን 2010 ዓም) በባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 04 የሚገኘው የቴሌ ቢሮ ላይ ፈንጂ ተጠምዶ ተገኘ
በባህርዳር ቀበሌ 04 በሚገኘው የቴሌ ቢሮ ውስጥ ፈንጂ ተጠምዶ በመገኘቱ ከመከላከያ ባለሙያ ተጠርቶ ሚስጥራዊነቱ በተጠበቀ ሁኔታ እንዲነሳ ተደርጓል። መረጃው ለህዝብ ይፋ እንዳይሆን የተደረገው ፣ ዜናውን ይፋ ማድረጉ የፀረ ሰላም ሀይሎችን በራሳችን አንደበት ሃይል እንዳላቸው አድርገን ለህዝብ ማስተዋወቅ ነው በሚል ምክንያት መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል። 
የተገኘው ፈንጅ ተቀጣጣይና ከባድ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል እንደነበር ምንጮች ገልጸዋል። 
በተመሳሳይ ቀበሌ 15 በሚገኝ ግሮሰሪ ውስጥ ዳሽን ቢራ ባዘጋጀው የደስታ ምሽት ( happy hour) ላይ “ዳሽን አይጠጠም” ብላችሁ ሁከት ፈጥራችሁዋል የተባሉ 3 ልጆች በ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል። ልጆቹ የተያዙት ቀበሌ 3 ውስጥ ሲሆን፣ በዚሁ ግሮሰሪ ውስጥ ቦንብ ተወርውሮ ሳይፈነዳ በመገኘቱ ልጆች እንዳደረጉት ተቆጥሮ ከያሉበት ተይዘው በ6ኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል።
ቴሌ ላይ የተጠመደው ፈንጅ እና ባለፈው ባህር ዳር አየር መንገድ የተገኘው ፈንጅ አንድ አይነት በመሆኑ የፖሊስ ኮሚሽን እና የደህንነት ባለስልጣናት ጠንካራ ጥቃት በቅርቡ ሊፈፀም ይችላል በሚል ስጋት ውስጥ ከቷቸዋል።
አዲሱ የደህንነት ሹም እዘዝ ዋሴ አጠቃላይ የደህንነት አባላትን ለስብሰባ ጠርቷል።

No comments:

Post a Comment