Tuesday, October 3, 2017

ለውትድርና የሚመዘገብ ሰው በመጥፋቱ በደላላ ማፈላለግ ተጀመረ

(ኢሳት ዜና–መስከረም 23/2010)ለውትድርና የሚመዘገብ ሰው በመጥፋቱ በደላላ ማፈላለግ ተጀመረ
በደቡብ ወሎ የተለያዩ ከተማዎች ለውትድርና የሚመዘገብ ወጣት በመጥፋቱ፣ ደላሎች ለውትድርና በሚያስመዘግቡት የሰው መጠን ገንዘብ እንደሚሰጣቸው ታውቋል። በተለያዩ መንገዶች ለሳምንታት የተደረገው ቅስቀሳ ውጤት አልባ መሆኑን ተከትሎ፣ደላሎቹ ባስመዘገቡዋቸው ወጣቶች ልጅ ገንዘብ እንደሚከፈላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
እነዚሁ ደላሎች በየሰፈሩ እየዞሩ የተለያዩ የቅስቀሳ ስራዎችን እየሰሩ ቢገኙም፣ እስካሁን አልተሳካላቸውም።
በተለያዩ ክልሎች ወጣቶችን ለውትድርና ለመመልመል የተደረገው ጥረት እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም አለመሳካቱን የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።

No comments:

Post a Comment