Tuesday, October 10, 2017

በገዋኔ በሶማሊ ልዩ ሃይልና በአፋር ህዝብ መካከል በተነሳ ግጭት 7 ሰዎች ቆሰሉ

ትናንት በገዋኔ ወረዳ በሮማ ቀበሌ በሶማሊ ልዩ ሃይል አባላት እና በአፋር ህዝብ መካከል በተነሳ ግጭት ከአፋር በኩል 3 ሰዎች ሲቆስሉ ከሶማሌ ልዩ ሃይል በኩል ደግሞ 4 ሰዎች ቆስለዋል። የሶማሊ ልዩ ሃይል አባላት በአካባቢው የሚኖሩ ኢሳዎችን በማበረታታትና ድጋፍ በመስጠት ወረራ ማካሄዳቸውን ምንጮች ገልጸዋል። የመከላከያ ሰራዊት በመሃል ገብቶ ግጭቱን ለማብረድ ቢችልም፣ በልዩ ሃይሉ ላይ የወሰደው እርምጃ ግን የለም።
በሌላ በኩል በመጋሌ ወረዳ አዲ ቀበሌ ትናንት አንድ የህወሃት ሹም መገደሉን ተከትሎ ፣ የትግራይ ልዩ ሃይል አባላት ከህዝቡ ጋር ተፋጠው እንደሚገኙ ታውቋል። (ኢሳት ዜና–መስከረም 30/2010)

No comments:

Post a Comment