Tuesday, October 31, 2017

የሃረሪ ብሄራዊ ሊግ መሪ ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

የሃረሪ ክልልን በበላይነት የሚመራው የሃረሪ ብሄራዊ ሊግ ( ሃብሊ) አባላት ከሁለት መከፈላቸው ታውቋል። የክልሉ ፕሬዚዳንት የሆኑትን አቶ ሙራድ አብዱላሂን የሚቃወሙ የድርጅቱ አባላት፣ ድርጅታቸው ባለፉት 25 ዓመታት በተከተለው ፖሊሲ ከተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እንዲጋጩ ያደረጋቸው በመሆኑና ዘላቂ ህልውናቸውን አደጋ ላይ የሚጥል እርምጃዎችን እየወሰደ በመሆኑ፣ ፕሬዚዳንቱ ከስልጣን እንዲወርዱ ድርጅቱም ፈርሶ ህዝቡ በሌሎች መንገዶች እንዲደራጅ እየጠየቁ ነው። እነዚህ አባላት፣ ችግሩ እየበዛ መሄዱንና የህልውና ስጋት እየደቀነባቸው መምጣቱን እየተናገሩ ነው። 
በህቡዕ የሚንቀሳቀሱት እነዚህ ተቃዋሚዎች፣ የተለያዩ የቅስቀሳ ጽሁፎችን እየበተኑ ነው። ሁሉንም የኢትዮጵያ ህዝብ ያማከለ ስርዓትና አደረጃጃት በክልላቸው እንዲፈጠር የሚጠይቁት አባላቱ፣ ይህን ማድረግ ካልተቻለ የውስጥ ትግላቸውን እንደሚገፉበት ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተለው የኢሳት ወኪል ገልጿል።

No comments:

Post a Comment