Tuesday, June 28, 2016

ፍርድ ቤት እነ አቶ አግባው ሰጠኝ እንዲከላከሉ ወሰነ

ሰኔ ፳፩ ( ሃያ አንድ ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14ኛ ወንጀል ችሎት በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ በተከሰሱ 16 ተከሳሾች ላይ ብይን የሰጠ ሲሆን፣   አቶ አግባው ሰጠኝን ጨምሮ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮነን፣  በላይነህ ሲሳይ፣  አለባቸው ማሞ፣  አወቀ ሞኝሆዴ ፣ ተስፋየ ታሪኩ፣  ቢሆነኝ አለነ፣ ተፈሪ ፈንታሁን ፣ፈረጀ ሙሉ፣  አትርሳው አስቻለው ፣ እንግዳው ቃኘው፣ አንጋው ተገኘ እና አባይ ዘውዱ ተከላከሉ ተብለዋል።

አቶ ዘሪሁን በሬ፣ ወርቅየ ምስጋናውና አማረ መስፍን መከላከል አያስፈልጋችሁም በሚል በነጻ ተሰናብተዋል። ፍርድ ቤቱ በ13ቱ ተከሳሾች ላይ የመከላኪያ ምስክር ለመስማት ለነሐሴ 18፣ 19 እና 20 ት ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ ይዟል። አቶ አግባው ሰጠኝ “ብሄሬ እየተጠቀሰ  ተሰድቤአለሁ፣ ከቤተሰብና ከጠበቃ ጋር እንዳልገናኝ ጨለማ ቤት ታስሬያለሁ” በሚል የረሃብ አድማ አድርጎ ነበር።

No comments:

Post a Comment