Wednesday, June 22, 2016

የተቀናሽ ሰራዊት አባላት በረንዳ ላይ እያደሩ መሆኑን ተናገሩ

ሰኔ  (አሥራ  አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሌሎች አገር ዜጎች ለተቀናሽ የሰራዊት አባላት ተገቢውን እንክብካቤ ሲያደርጉ፣ በኢትዮጵያ ግን ማረፊያ ጎጆ እንኳን በማጣታቸው በረንዳ ላይ እየተጣሉ መሆኑን የተቀናሽ ሰራዊት አባላት ተናግረዋል።

በባህርዳር በርካታ የተቀናሽ ሰራዊት አባላት ያሉ ሲሆን ብዙዎቹ በረንዳ ላይ ያድራሉ። “ሰራዊቱ አካሉን አጥቶና ተጎድቶ እያለ” መኖሪያ ቤት እንኳን ማግኘት አልቻለም የሚሉት የተቀናሽ ሰራዊት አባላት፣ አቤቱታቸውን የሚሰማላቸው ሰው በማጣታቸው እንደሚበሳጩ ይገልጻሉ።
መስተዳድሩ የመንግስት ቤቶችን በአግባቡ ለህዝብ በሚጠቅም መልኩ አለማስተዳደሩ በርካታ ዜጎች በርንዳ ላይ እንዲያወድቁ አድርጎአቸዋል።

No comments:

Post a Comment