Friday, June 24, 2016

መምህራን በግዳጅ የመምህራንን ቀን ሊያከብሩ ነው

ሰኔ  (አሥራ  ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሰኔ 22 ቀን 2008 ዓም በሚከበረው በአል ላይ መምህራን በግዳጅ በቦታው ተገኝተው እንዲያከብሩ ታዘዋል።

የመምራን ነጻነት ባልተከበረበት ሁኔታ፣ የመምህራንን ቀን ማክበሩ ትርጉም የለውም በሚል ተቃውሞ ያነሱ መምህራን “ ትታሰራላችሁ” የሚል ማስፈራሪያ ደርሷቸዋል። መንግስት ከመምህራን ሊደርስበት የሚችለውን ተቃውሞ በመፍራት ሰሞኑን የደሞዝ ጭማሪ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ጭማሪው መታወጁን ተከትሎ በቤት ኪራይና በእቃዎች ላይ ዋጋ ይጨምራል በሚል መምህራን ፍርሃታቸውን እየገለጹ ነው።
ለደህነታቸው በሚል ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ መምህራን እንደገለጹት፣ ገዢው ፓርቲ በማስፈራራት እና የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን ለመስጠት ቃል በመግባት መምህራንን ከጎኑ ለማሰልፍ ጥረት ቢያደርግም፣ በርካታ መምህራን ግን አሁንም “ ከሁሉም በላይ ነጻነታችንን እንፈልጋለን” በሚል የድርጅቱ አባል ለመሆን ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment