Thursday, April 28, 2016

ተመድና የኢትዮጵያ መንግስት በጋራ ለምግብ እርዳታ ገቢ የማሰባሰብ ዘመቻ ጀመሩ

ኢሳት (ሚያዚያ 19 ፥ 2008)

በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ ለተጋለጡ ሰዎች የሚያስፈልገው ድጋፍ በበቂ ሁኔታ አለመገኘቱን ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶችና መንግስት በለጋሽ ሃገራት በመዘዋወር ገቢ የማሰባሰብ ዘመቻ ጀመሩ።

ይኸው ማክሰኞ በኖርዌይ መዲና ኦስሎ ከተማ የተጀመረው ድጋፍን የማሰባሰብ ዘመቻው በስዊዘርላንድ ጄኔቫና በዚህ በአሜሪካ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና መቀመጫ በሆነችው የኒውዮርክ ከተማ እንደሚካሄድም ታውቋል።
ከ10 ሚሊዮን ለሚበልጡ ተረጂዎች ወደ 1.4 ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ቢያስፈልግም፣ ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት መኖሩን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል።

No comments:

Post a Comment