Thursday, July 9, 2015

የጦር ሃይሎች ኢታማዦር ሹም ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ፣ ጠ/ሚኒስትሩን ጨምሮ ከፍተኛ የኢህአዴግ የጦር አዛዦች በተገኙበት የወታደራዊ ጥቅል አቋማቸውን አቅርበዋል

ሐምሌ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የጦር ሃይሎች ኢታማዦር ሹም ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ፣ ጠ/ሚኒስትሩን ጨምሮ ከፍተኛ የኢህአዴግ የጦር አዛዦች በተገኙበት የወታደራዊ ጥቅል አቋማቸውን አቅርበዋል። በከፍተኛ ሚስጢር በተካሄደው ስብሰባ ላይ ፣ ጄ/ል ሳሞራ " ጦራችን ከጊዜው ጋር እየዘመነ አይደለም፣ የታንኮቻችን አቅም ያረጀ ነው፣ ተዋጊ አውሮፕላኖቻችን ከገበያ የወጡ ናቸው፣ መቀየሪያ እቃዎቻቸው ( ስፔር ፓርትስ) ከገበያ እየወጡና እየጠፉ ነው። " ብለዋል። 349 ሺ 571 የሰራዊት አባላት እንዳሉ የገለጹት ጄ/ል ሳሞራ፣ የምድር ሃይል በ10 ክፍለጦሮችና 61 ብርጌዶች መዋቀራቸውን ተናግረዋል። ጠረፍ ጠባቂ የሰው ሃይል 13 ሺ 564 ሲሆን፣ ቀዳሚ ኮር ተብሎ የሚወሰደው 2 ሺ 300 ፣ ማዕከላዊ የደህንነት ኃይል 349 ሺ 571 እንዲሁም ብሄራዊ ጠባቂ ጦር 35 ሺ 000 ድንበር ተከላካይ ደግሞ 11 ሺ 578 መሆኑን ጀኔራል ሳሞራ ገልጸዋል። በምድር ጦር ሃይል በታንኮች ምድብ ከፍተኛ ደረጃ ያላቸው ኤም 1 ኤ 1 ብዛት 537 ሲሆን፣ አገልግሎት መስጠት የሚችሉት 321 ዱ ናቸው፡፡ አገሪቱ መለስተኛ እና አነሰተኛ ኤም 60 ኤ 3 ፣ 234 ሲኖሩዋት በትክክል መስራት የሚችሉት 198 ናቸው። 301 የሚሆኑ ኤም 6 ኤ 1 የጦር መሳሪያ ሲኖሩ መስራት የሚችሉት 299 ዱ ናቸው ፡፡ ከ253 ቲ-62 ታንኮች መካከል መስራት የሚችሉት 211 መሆናቸውን፣ ካሉት 203 ቲ- 55 መለስተኛ አነስተኛ የምድር ጦር ታንኮች ውስጥ 119 ኙ መስራት እንደሚችሉ ጀኔራሉ ገልጸዋል። የቅኝት አውሮፕላኖቻችን አቅም ውስን ነው ያሉት ጀኔራል ሳሞራ የኑስ በአሁኑ ስዓት 7 የቅኝት አውሮፕላኖቻችንን ይዘን መንቀሳቀስ ከፍተኛ ጉዳት በመሆኑ ፤ በአዲሱ የሀገሪቱ በጀት ከግብርና ፤ ከጤና ሴክተር ከተበጀተላቸው የስራ ማስኬጃ 15 በመቶ የሚሰጡት ወደ 20 በመቶ ማደግ አለበት ብለዋል፡፡ ሞዴላቸወ ኤፒሲኤስ ኤም 113 ኤ 2 የኤኤፍ ቪኤስ ተሽከርካሪዎች በቁጥር 1560 ሲሆኑ አገልግሎት መስጠት የሚችሉት 678 ብቻ ናቸው፡፡ አይኤፍ ቪኤስ ሞዴል የሆኑ - ዋይ ፒአር -765 ተሸከርካሪዎች፣ በቁጥር 314 ፤ ቢኤምፒ-1 በቁጥር 189 ፤ ቪ-150 /ቪ-300 ኮምንዶ በቁጥር 186 እንደሚገኙም ገልጸዋል። በቅኝት መሳሪያነት ቢአርዲኤም -1 በቁጥር 158፣ ቢቲአር-40/152 የቅኝት ሞዴል 523 አሉን ያሉት ጄ/ል ሳሞራ፣ በቀጣይ የዘመኑ ቢቲአር -50 -ፒኬኤም በቁጥር 156 ፣ዋይፒአር-765 በቁጥር 326 እንደሚያስፈልጉ ገልጸዋል። 156 የሚሆኑ በመድፍ ጦር መሳሪያ ሞዴላቸው 155 ሚሊ ሜትር ኤም 109 ኤ2 ያሉ ሲሆን አገልግሎት መስጠት የሚችሉት 99 ብቻ ናቸው፡፡ 87 ፣ 122 ሚ ሜ ኤስፒ ያሉ ሲሆን፣ ሀሉም አገልግሎት መስጠት ይችላሉ፡፡ ሞዴላቸው 130 ሚሊ ሜትር ኤም-46/ ፣ 122 ሚሜ ዲ-130 የግዥ ጥያቄ ቀርቦ በድርድር ላይ ነው፡፤ ሞዴላቸው 155 ሚሜ ጂኤች 52 ኤፒዩ እና 153 ሚሜ ኤም 109 ኤ2/ኤ3 በሀገር ውስጥ ለመሸፈን መለዋወጫዎችን ከውጭ በማስመጣት እየተሰሩ ያሉ የመድፍ አይነት መሆናቸውንም ጄኔራሉ ገልጸዋል። አገሪቱ 3፣ አርቲላሪና ሞርተር አመልካች ራዳሮች ኤኤን/ቲፒ ኪው-36 ሲኖሯት፣ ኤኤን/ቲፒ ኪው-37 በቀጣይ ሶስት ወራት ወደብ ይደርሳሉ ተብሏል። ሌሎች በርካታ የጦር መሳሪያዎችና የተሽከርካሪዎችን ብዛት በዝርዝር የገለጹት የመከላከያ ምንጮች፣ ኢሳት ለዜና በሚመች መልኩ ያቀረበው፣ ጄ/ል ሳሞራ ካቀረቡት ሪፖርት በጣም አነስተኛውን ነው። ጄ/ል ሳሞራ ሪፖርቱን ካቀረቡ በሁዋላ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ‹‹እኔ ስለጦርነት ምንም አይነት ኖሃው ( አውቀቱ) የለኝም፣ የግዥ ፍላጎቱን አፀድቃለሁ፣ እናንተ ብቻ ይሆናል የምትሉትን አቅርቡልኝ" የሚል አጭር መልስ ሰጥተዋል። በወይይቱ ወቅት የተነሱ የኢህአዴግ ሰራዊት የስልጠና እና ግንኙነት አውሮፕላኖች አይነት እና መጠን ፤አየር ሃይሉ አሉት የተባለውን የጦር መሳሪያ ፤ አየር መካላከል እና የጦር ሃይሉን ስርጭት እንዲሁም፣ የጦር ሃይል ሰፈሮች ፤ የአየር መከላከያ ዘዴዎች ፤ መጠገኛዎች እና የጦር መሳሪያ ማከማቻ ቦታዎች ፤ የጦር አወሮፕላኖቻቸውን የወጊያ ብቃት እንደምናቀርብ ለመግለጽ እንወዳለን። ኢሳት መረጃውን ላቀረቡልን የዘወትር ምንጮች ያለውን ከፍተና ምስጋና ለማቅረብ ይወዳል፡፡


No comments:

Post a Comment