Friday, July 31, 2015

የአዲስ አበባ መንገዶች በጎርፉ እየተጥለቀለቁ ነው

ሐምሌ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዲስ አበባ ጎዳናዎች የፍሳሽ ማስወገጃ ትቦዎች የሌላቸው እስኪመስል ድረስ እግረኞች ብቻ ሳይሆኑ አሽከርካሪዎችም ጭምር መንገድ ለማቋረጥ ሲሳናቸው ተስተውሏል። በርካታ የአዲስ አበባ መንገዶች ከዓመት እስከ ዓመት ተመሳሳይ ችግሮች ቢስተዋልባቸውም መንገድ ትራንስፓርት የፍሳሽ ማስወገጃዎችን በመስራትና የተበላሹትን ጠግኖ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ አልቻለም። የከተማው ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ቢያሰሙም ችግራቸውን ሰምቶ መፍትሔ የሚሰጣቸው አካል ግን እስከ አሁን ድረስ ባለማግኘታቸው፣ በዝናብ ወቅት ከፍተኛ የሆነ ችግሮች እንዳሉባቸው በገሃድ መታየት መጀመሩን ነዋሪዎች ይናገራሉ።

No comments:

Post a Comment