Tuesday, July 14, 2015

ርዮትን ተክታ ወህኒ የወረደች የጣይቱ ልጅ – የሚሊዮኖች ድምጽ

አስቴር ስዩም ትባላለች ። በጎንደር ምእራብ አርማጭሆ የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አመራር አባል ነች። የማስተርስ ዲግሪዋን ከዩኒቨርሲቲ በማእረግ ተቀብላለች፡ ላመነችበት ነገር ወደኋላ የማትል የጣይቱ ልጅ መሆኗን ለመረዳት ብዙ ጊዜ አላስፈለግም። ስትናገር ቁጥብ ናት ። ከመናገር ማዳመጥን ታስቀድማለች ።ታዲያ ይህች ባለትዳርና አንድ ልጅ እናት የሆነች የነፃነት ታጋይ፣ ከገዢው መደብ ካድሬዎች፣ የተለያዩ ማባበያዎች ቢቀርብላትም ሳይማር ያስተማረኝን እና ገዢዎቻችን ደሀ ያደረጉትን የሀገሬን ገበሬ ውለታ ለእናንተ አጎብድጄ አልክድም። የፍትህ ፀሀይ ወጥታ የሰላም አየር እስክንተነፍስ ድረስ ትግሌን አላቋርጥም” በማለቷ በተለመደው የፈጠራ ከሱ ወህኒ ተጥላለች ክብር ለአስቴር ስዩም 

No comments:

Post a Comment