Wednesday, July 29, 2015

የበረከት በህይወት መኖር እያጠራጠረ ነው! መሞቱን የሚናገሩም ኣሉ


ጅዳ ሳውዲ አረቢያ ለህክምና በድብቅ ገብተው የልብ በሽታ ህክምና የተደረገላቸው የመንግስት ከፍተኛ ሹም በህይወት መኖራቸውን እንደ ሚጠራጠሩ ከሆስፒታሉ የሚወጡ ምስጢራዊ ምንጮች አረጋገጡ፡፤ በልብ በሽታ የሚሰቃዩት አቶ በረከት ለህክምና ጅዳ ሳውዲ አረቢያ የሚገኝ አንድ ሆስፒታል ህክምናቸውን ተከታትለው ወደ ሃገር ከተመለሱ ወዲህ የጤንነታቸው ሁኔታ እንብዛም ባለመስተካከሉ አመት ባልሞላ ግዜ ውስጥ ለሁለተኛ ዙር ወደ ሳውዲ አረቢያ « ብግሻን» ሪፈራል ሆስፒታል ማቅናታቸው የታወሳል ፡፤ አቶ በረከት ስሞኦን ከብስጭት ከተለያዩ የአልኮል መጠጦችና ከአይምሮ አደንዛዥ እጽ እንዲርቁ ተመክረው ጤንነታቸው አሰተማማኝ ደረጃ እስኪ ደርስ የዶክተሮች ቅርብ ክትትልእንደሚያሻው ተነግሯቸው በቀጠሮ ቢሸኙም የቀጠሮ ግዜያቸውን አክብረው ዶክተሮቻቸው ጋር መቀረብ አለመቻላቸውን የሚገልጹ የሆስፒታሉ ምንጮች ባለስልጣኑ በህይወት መኖራቸውን ይጠራጠራሉ።
ጅዳ « ብግሻን» ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ የልብ ቧንቧ ማስፋት ህክምና የተደረገላቸው የኢ.ህ.አ.ዴ.ጉ ሹም የጤነነት ሁኔታ የሚጠበቀውን ያህል ለወጥ አስይቶ እንዳል ነበር ሙያዊ ትንታኔ የሚሰጡ ምስጢራዊ የሆስፒታሉ ምንጮች በሽታው የልብ እንደ መሆኑ መጠን ባልታሰበ ግዜ ባለስልጣኑን ለሞት ሊዳርጋቸው እንደሚችል ከአቶ በረከት ጋር ለመጣ አስታማሚ ገልጸው እንደ ነበር ያስታውሳሉ። በዚህም መስረት አቶ በረከት ስሞዖን ለሶስተኛ ግዜ ልባቸውን መታየት እንዳለባቸው ተነግሮቸው ቢሰናበቱም በቀጠሮ ቀን ተገኝተው ህክምናቸውን መከታተል ባለመቻላቸው በጤናቸው ላይ ሊያደርስ የሚችለው ተጽዕኖ ከፍተኛ መሆኑን የሚያሳየው የምርመራ ውጤት በረከት ሌላ ሃገር ለህክምና ሄዶ ካልሆነ በቀር አሁን ባሉበት ሁኔታ የልብ በሽታው ለአደጋ ሊዳርጋቸው እንደሚችል በመጥቀስ ባለስልጣኑ በህይወት የሉም የሚለውን ጥርጣሬ ያጠናክራሉ ። በአቶ በረከት ስሞን ጤንነት ዙሪያ ከጅዳ «ብግሻን» ሆስፒታል ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ጥረት እናደርጋለን ።

No comments:

Post a Comment