Thursday, July 7, 2016

የተመድ የምግብና የእርሻ ክፍል በጎርፍ ለተጎዱት ዜጎች ተጨማሪ ገንዘብ ጠየቀ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ እና የእርሻ ክፍል በቅርቡ በተከሰተው ረሃብ የተጎዱ ዜጎች ሳያገግሙ በድጋሜ በጎርፍ በመጠቃታቸው ለመስከረም ወር ተጨማሪ የ3 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ጠይቋል።

ድርጅቱ የኢትዮጵያን የጎርፍ አደጋ መከላከል ግብረሃይልን ጠቅሶ እንደዘገበው በጎርፉ ምክንያት 690 ሺ ተፈናቅለዋል።
55 ሺ ሄክታር መሬትም በጎርፍ መጥለቅለቁን ድርጅቱ አስታውቋል።
በድርቁ የተጎዱ ዜጎች ወደ ነበሩበት ቦታ ለመመለስ በትንሹ ሁለት አመት ያስፈልጋቸዋል።
ድርጅቱ የውሃ አቅርቦትን ለመጨመር ተጨማሪ 2 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፍልገውም ገልጿል።

No comments:

Post a Comment