Friday, July 22, 2016

በኦሮሚያ ሕዝባዊው አመጽ እየተቀጣጠለ ነው – በአምቦ ተቃውሞ ተነሳ

(ዘ-ሐበሻ) ትናንት በምስራቅ ሐረርጌ ሂርን ከተማ ውስጥ ባለችው ዲንቁ አካባቢ ወጣቶች እና ታዳጊዎች ከአዋቂዎች ጋር በመሆን ሕዝቡን ሲያሰማ – በተመሳሳይ ቀን በቦረና ተልታሌ አካባቢም እንዲሁ ሕዝቡ እጁን ወደላይ በማጣመር ሲቃወም የዋለ ሲሆን ይህ ዜና እየተጠናቀረ ባለበት ወቅት በአምቦም ተመሳሳይ ተቃውሞ መነሳቱ ታውቋል::
በኦሮሚያ የተጀመረው ሕዝባዊ ቁጣ በየከተማው በተለያዩ ቀናት ላለፉት 8 ወራት ሲካሄድ ቆይቷል:: በተለይም በሃገር ቤት የሚኖሩ ትግሉን ሊመሩ ይችላሉ የተባሉ ታዋቂ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን በማሰር እንዲሁም ከ400 በላይ ሰላማዊ ዜጎችን በመግደል በኦሮሚያ የተከሰተውን ሕዝባዊ አመጽ ለማብረድ ስር ዓቱ ቢሞክርም አሁንም የሕዝቡ ቁጣ በየቦታው እየተቀጣጠለ ይገኛል::
ዛሬ በአምቦ ከተማ በርካታ ሰዎች ተቃውሟቸውን በማሰማት ከአጋዚ ሰራዊት ጋር ተፋጠዋል:: ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በአምቦ በተከሰተው ሕዝባዊ ተቃውሞ ስለተጎዳ ሰውና ንብረት የደረሰን መረጃ የለም::

No comments:

Post a Comment