Monday, December 8, 2014

አመራሮቹ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

በሰላማዊ ሰልፉ ታፍሰው የታሰሩት የትብብሩ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ዛሬ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ይቀርባሉ፡፡ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ ኤራጫፎ ኤርዴሎ፣ አለሳ መንገሻን ጨምሮ በሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ታሳሪዎቹ እንደሚያነክሱ ማረጋገጥ ችለናል፡፡

በተመሳሳይ ከሰልፉ በፊት ታፍና ቤላ አካባቢ ታስራ የነበረችው ወይንሸት ንጉሴ ሾላ ደርሳለች፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ኮተቤ ፖሊስ መምሪያ ታስረው የሚገኙት 10 ታሳሪዎች ሾላ ምድብ እንዲሁም ጨርቆስ ታስረው የሚገኙት ቄራ ወይንም ሜክሲኮ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡


No comments:

Post a Comment