Thursday, December 4, 2014

አዲስ አበባ በተበተነ ወረቀት ተሸፍና አደረች

        አዲስ አበባ በተበተነ ወረቀት ተሸፍና አደረች። ሚሊዮኖች የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በየመንገዱና በየአደባባዩ የተበተኑ ወረቀቶችን እያነበቡ ደስታቸውን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ። የ24 ሰዓቱ የአዳር ሰልፍ ቅስቀሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል። እማኞች እንደሚሉት በተለይ ከጎተራ እስከ ሳር ቤት ባለው መንገድ ላይ የሚቀሳቀስ ሰው በሙሉ የተበተነው ወረቀት መልዕክትና የፊታችን እሁድ የሚደረገው የ24 ሰዓት ሰልፍ ላይ እንደሚገኝ በደስታ እየገለጸ ይገኛል። ባልተለመደ መልኩ አዲስ አበባ ከባድ መሳሪያ በታጠቁ የወያኔ ሰራዊት ተሞልታለች። ወያኔ ራሱ በፍርሃት በፈጠረው ሽብር ተርበትብቷል። ይህ ደግሞ የስርዓቱን ፍርሃት ደረጃና መውደቂያው መቃረቡን ያሳያል።
የውጭ ሃገር የመገናኛ ብዙሃን ያሰማራቸው ፎቶ አንሺዎች ከተማ ውስጥ ያለውን እንቅስቃሴ በድብቅ ከ100-300 ሜትር ርቀት አካባቢ ሆነው በተለይ የአዲስ አበባ ፖሊስንና ታጣቂዎችን በልዩ ካሜራዎች ሲቀርጹ ታይተዋል።

No comments:

Post a Comment